Sunday, November 19, 2006
Friday, November 17, 2006
ወደድኩሽ ውደጂኝ
ብዕር ከወረቀት
ማሳሳም ተስኖኝ
የመውደድ ደብዳቤ
አልወለድ ብሎኝ
ቀለም ወረቀት ላይ
ገና አላሸበረቀ
ቃላት በ ቃላት ላይ
ቃልን እያረቀ ::
አንዱ ቃል ከ ሌላው
ልቤ ውስጥ ሲራኮት
ደብዳቤ ለመፃፍ
ለአካል ሙናዬ ውቢት
ሞቀልኝ ገበያው
የፍቅር ቃላቱ
ሲተራመስ አየሁ
ቅኔ ም በአይነት አይነቱ
የቃላት ዕሩምታው
አላከትም ቢለኝ
'እኔን ምረጥ እኔን '
የሚሉም መሰልኝ ::
ሁሉም ቆንጆ መላክ
ብቃት የታደሉ
'እኔ ልሸከም ፍቅር
እኔን ምረጥ ' ያሉ
ጉጉታቸው ልቆ
"እኔ ልቅደም ' 'የለም እኔ ' ቢሉ
ከ ወደድኩሽ _ውደጂኝ
ጭራሽ ! አይስተካከሉ ::
ማሳሳም ተስኖኝ
የመውደድ ደብዳቤ
አልወለድ ብሎኝ
ቀለም ወረቀት ላይ
ገና አላሸበረቀ
ቃላት በ ቃላት ላይ
ቃልን እያረቀ ::
አንዱ ቃል ከ ሌላው
ልቤ ውስጥ ሲራኮት
ደብዳቤ ለመፃፍ
ለአካል ሙናዬ ውቢት
ሞቀልኝ ገበያው
የፍቅር ቃላቱ
ሲተራመስ አየሁ
ቅኔ ም በአይነት አይነቱ
የቃላት ዕሩምታው
አላከትም ቢለኝ
'እኔን ምረጥ እኔን '
የሚሉም መሰልኝ ::
ሁሉም ቆንጆ መላክ
ብቃት የታደሉ
'እኔ ልሸከም ፍቅር
እኔን ምረጥ ' ያሉ
ጉጉታቸው ልቆ
"እኔ ልቅደም ' 'የለም እኔ ' ቢሉ
ከ ወደድኩሽ _ውደጂኝ
ጭራሽ ! አይስተካከሉ ::
Wednesday, November 15, 2006
Spyining on each other
When I look at
flowers bloom fine
Inwhich Beauties,
beautyfully define
There I see your smile
Painting my soul,
as it's so vital.
When I look up at
the heaven,
Seductive horizon
I see you there as the sun
Bathing my whole body,
With such a love-shine.
When I look at
the river,
Pure clear water
There I see your reflection,
As an angle's fire.
As though you and I
Are the earth and the sky
Spying on each other
Every now and then,
And forever and ever.
bati
flowers bloom fine
Inwhich Beauties,
beautyfully define
There I see your smile
Painting my soul,
as it's so vital.
When I look up at
the heaven,
Seductive horizon
I see you there as the sun
Bathing my whole body,
With such a love-shine.
When I look at
the river,
Pure clear water
There I see your reflection,
As an angle's fire.
As though you and I
Are the earth and the sky
Spying on each other
Every now and then,
And forever and ever.
bati
Monday, November 13, 2006
ጌታ
ፈጣሪ ቢቆጣ
አሣር በዛ ጣጣ
እኛ ባመጣነው
ሰውን አምልከነው
ጌታዬ ብንለው
ይኸው ይኸው
ባሀገር ሟቹ ህዝብ ላይ .....
ባንዳን አንሰራራው ::
ምድር ዛፍ _ ቅጠሉ
እምቢ አለ ሁሉ
ከበረትም ከብቱ
ካውድማ ላይ ምርቱ
የለም ረድኤቱ
ጥሮና ግሮ ሰው
አንዲት ቁና ጠፋ ..........
ጎተራም ዕራበው ::
''ንጉሱ ''ም ሰው ናቀ
ባምላክ ተሳለቀ
ሳቀ ሳቀ ሳቀ
ግና ........
ሰው ተንሰቀሰቀ ::
መዋደድ ጠፋ
ልጅ አባቱን ገፋ
አባት ልጁን ተፋ
ምን ይኖረን ተስፋ
ይኽ አምላክ የለሹ .........
ጨርሶ እስኪጠፋ ::
ባምላክ ታምኖ ወጥቶ
ጠላትን ድል ነስቶ
አንገቱን ያልደፋ
በፋሺሽት ለከፋ
ምነው ዛሬ ምነው .......
ባንዳን አጥፊ ጠፋ ?
ባይኖር ከገበታ
በዕጦት ቢንገላታ
በፋሺሽቶች ፈንታ
ጌታዬ አለው በርታ !
ሀገር አ ድ ሚ ዉን ሰው .....
ያን ምላሰ መንታ ::
አሣር በዛ ጣጣ
እኛ ባመጣነው
ሰውን አምልከነው
ጌታዬ ብንለው
ይኸው ይኸው
ባሀገር ሟቹ ህዝብ ላይ .....
ባንዳን አንሰራራው ::
ምድር ዛፍ _ ቅጠሉ
እምቢ አለ ሁሉ
ከበረትም ከብቱ
ካውድማ ላይ ምርቱ
የለም ረድኤቱ
ጥሮና ግሮ ሰው
አንዲት ቁና ጠፋ ..........
ጎተራም ዕራበው ::
''ንጉሱ ''ም ሰው ናቀ
ባምላክ ተሳለቀ
ሳቀ ሳቀ ሳቀ
ግና ........
ሰው ተንሰቀሰቀ ::
መዋደድ ጠፋ
ልጅ አባቱን ገፋ
አባት ልጁን ተፋ
ምን ይኖረን ተስፋ
ይኽ አምላክ የለሹ .........
ጨርሶ እስኪጠፋ ::
ባምላክ ታምኖ ወጥቶ
ጠላትን ድል ነስቶ
አንገቱን ያልደፋ
በፋሺሽት ለከፋ
ምነው ዛሬ ምነው .......
ባንዳን አጥፊ ጠፋ ?
ባይኖር ከገበታ
በዕጦት ቢንገላታ
በፋሺሽቶች ፈንታ
ጌታዬ አለው በርታ !
ሀገር አ ድ ሚ ዉን ሰው .....
ያን ምላሰ መንታ ::
Wednesday, November 08, 2006
ምጥን ቀጭን ሽሮ
ምጥን ቀጭን ሽሮ
ኧረ ጉድ ዘንድሮ
ተወዶ ተፈቅሮ
ሰው አይፀድቅ ቆንጥሮ ::
ከሜኑው በፎቶ
ድርት ብሎ ኮርቶ
ታየ ኩሩው ሽሮ
ዶኬ ጥንብርብሮ
ክብሩን አስከብሮ ::
ገላመጥነው ድሮ
አመድ ነዥን ሽሮ
አሁን ተቀይሮ
በእጅግ ተሞሽሮ
እንጀራው ላይ ሰፍሮ
በአይንም ተበላ .......
ላፍ ደባሪው ሽሮ ::
''ሽሮን ሲያታልሏት
ፕሮቲን ነሽ አልዋት ''
ስንል ያፌዝንበት
ይኸው ቀን ወቶሎት
ተናፈቀ በዉነት
እርጉዝ እስኪያስገድድ
ዕምሮት እስኪያስወርድ
ተወዶ እንደጉድ !!
አበው እንዳሉት
ሽሮንም ስናየው፣
ቅል ድንጋይ ይሠብራል
ለሁሉም ጊዜ አለው ::
ኧረ ጉድ ዘንድሮ
ተወዶ ተፈቅሮ
ሰው አይፀድቅ ቆንጥሮ ::
ከሜኑው በፎቶ
ድርት ብሎ ኮርቶ
ታየ ኩሩው ሽሮ
ዶኬ ጥንብርብሮ
ክብሩን አስከብሮ ::
ገላመጥነው ድሮ
አመድ ነዥን ሽሮ
አሁን ተቀይሮ
በእጅግ ተሞሽሮ
እንጀራው ላይ ሰፍሮ
በአይንም ተበላ .......
ላፍ ደባሪው ሽሮ ::
''ሽሮን ሲያታልሏት
ፕሮቲን ነሽ አልዋት ''
ስንል ያፌዝንበት
ይኸው ቀን ወቶሎት
ተናፈቀ በዉነት
እርጉዝ እስኪያስገድድ
ዕምሮት እስኪያስወርድ
ተወዶ እንደጉድ !!
አበው እንዳሉት
ሽሮንም ስናየው፣
ቅል ድንጋይ ይሠብራል
ለሁሉም ጊዜ አለው ::
Tuesday, November 07, 2006
ማር ቀረ
ማር ቀረ
በዉነት ማር ቀረ
ስኳር ሽቅብ ናረ ::
በረሀብ እንዳይረግፍ፣
ፅዳቱ እንዳይጎድፍ፣
ዘብ ብትቆም ደጃፍ፣
ዕጥር አርጋው በክንፍ፣
ከቶ አንዳች እንዳያልፍ፣
ከሠራተኛው ረድፍ፣
ገፍቶ ለመጣው ነው ........
ንቢት ብትናደፍ ::
ስለንቦች .......
አኃዝ የለሹ ንብ
ሲርመሰመስ ያለው፣
ሎሌ ለንግስቱ
ለኑሮ መከታው ::
ጥንቁቅ ናት እሷም
እንዲሠምር ሰልፉ ፣
ጥጋብ እንዲበዛ
ማር ሞልቶ እስካፉ፣
ሟች ናት ለቀፎዋ
አይደለችም ክፉ ::
ስለንቦች ......
አይታወቅ በይፋ ፣
ንብ በንብ ሲከፋ፣
አዬ !
ስንቱ አቀረቀረ ፣
የዝንብ ኑሮን ኖረ ፣
በንብ ነኝ ተብዬው ......
ንቡ ተባረረ፣
ቀፎም ጦም አደረ፣
በዉነት ማር ቀረ ! ፣
ስኳር ሽቅብ ናረ ::
በዉነት ማር ቀረ
ስኳር ሽቅብ ናረ ::
በረሀብ እንዳይረግፍ፣
ፅዳቱ እንዳይጎድፍ፣
ዘብ ብትቆም ደጃፍ፣
ዕጥር አርጋው በክንፍ፣
ከቶ አንዳች እንዳያልፍ፣
ከሠራተኛው ረድፍ፣
ገፍቶ ለመጣው ነው ........
ንቢት ብትናደፍ ::
ስለንቦች .......
አኃዝ የለሹ ንብ
ሲርመሰመስ ያለው፣
ሎሌ ለንግስቱ
ለኑሮ መከታው ::
ጥንቁቅ ናት እሷም
እንዲሠምር ሰልፉ ፣
ጥጋብ እንዲበዛ
ማር ሞልቶ እስካፉ፣
ሟች ናት ለቀፎዋ
አይደለችም ክፉ ::
ስለንቦች ......
አይታወቅ በይፋ ፣
ንብ በንብ ሲከፋ፣
አዬ !
ስንቱ አቀረቀረ ፣
የዝንብ ኑሮን ኖረ ፣
በንብ ነኝ ተብዬው ......
ንቡ ተባረረ፣
ቀፎም ጦም አደረ፣
በዉነት ማር ቀረ ! ፣
ስኳር ሽቅብ ናረ ::
Thursday, November 02, 2006
As Pure As Babies
As pure as babies
and free used to be
I,
Free,
in telling the truth,
but not a single
lie.
Now!
my peace
is running out and
Saying to me
bye bye,
God,
as Pure as babies
let me live
and die.
and free used to be
I,
Free,
in telling the truth,
but not a single
lie.
Now!
my peace
is running out and
Saying to me
bye bye,
God,
as Pure as babies
let me live
and die.
Monday, October 30, 2006
አበባ _ከ _ማሩ
አበባ _ከ _ማሩ
መላዕክት ስም አወጡ
ያይኔ አበባ አልዋት
በዕውነት ከአበባ
በላጭ መስህብ አላት ::
ልዩ ሰው ለኔማ
ደማቅ ፍቅር አበባ
ፅጌረዳን ውበት
ብቅ ያለች ደራርባ ::
እማኝ ህዋሶቼ
ሲታጠንዋት ዋሉ
በመአዛዋ ርቀው
ጠፍቶባቸው ውሉ ::
ለደማቅዋ አበባ
ንብ ሁን አለኝ ልቤ
ቅስም ቅምስ ላደርግ
አይቀርቡን ቀርቤ ::
ልቤ ግን ቸኮለ
ሊሆን የማር ቀፎ
በእንኳን ደህና መጣሽ
ሊያሳድራት አቅፎ
አባባ _ከ _ማሩ
ቢታየው ተንሳፎ ::
መላዕክት ስም አወጡ
ያይኔ አበባ አልዋት
በዕውነት ከአበባ
በላጭ መስህብ አላት ::
ልዩ ሰው ለኔማ
ደማቅ ፍቅር አበባ
ፅጌረዳን ውበት
ብቅ ያለች ደራርባ ::
እማኝ ህዋሶቼ
ሲታጠንዋት ዋሉ
በመአዛዋ ርቀው
ጠፍቶባቸው ውሉ ::
ለደማቅዋ አበባ
ንብ ሁን አለኝ ልቤ
ቅስም ቅምስ ላደርግ
አይቀርቡን ቀርቤ ::
ልቤ ግን ቸኮለ
ሊሆን የማር ቀፎ
በእንኳን ደህና መጣሽ
ሊያሳድራት አቅፎ
አባባ _ከ _ማሩ
ቢታየው ተንሳፎ ::
Tuesday, October 17, 2006
Friday, October 13, 2006
ማን ይሉት ቋንቋው
Posted: Tue Jan 31, 2006 11:58 pm Post subject: ማን ይሉት ቋንቋው
ማን ይሉት ቋንቋው
ማን ይሉት ቋንቋው
ውበትሽን መግለጫ ,
ከዕንቁ የላቀ ዕንቁን
ትንታኔ መስጫ
ዝምታ ነው መልሴ
ስላንቺ ብጠየቅ ,
ምንም ቃል የለኝ
ፀጋሽን ለማድነቅ
ገነት ገነትዬ
ልበል በጥቅሉ ,
ቋንቋ አልተፈጠረም
የሚገልፅሽ ቃሉ
እንጎቻሽ ሸጋ
ፍሬሽም ጣፋጭ ,
ትትና ደግነት
ከልብ የሚያመነጭ
ማን ይሉት ቋንቋው
አንቺን የመግለጫ ,
ከፍቅር የላቀ ፍቅርን
ትንታኔ መስጫ
ገኒዬ ገኒዬ
አለሁልህ በይኝ ,
በፈጠርሽ አምላክ
ቋንቋሽን አውሽኝ ,
ከ 'አፈቀርኩ ' ሽ ዕሚልቅ
ተንፍሼ ይውጣልኝ ::
ማን ይሉት ቋንቋው
ማን ይሉት ቋንቋው
ውበትሽን መግለጫ ,
ከዕንቁ የላቀ ዕንቁን
ትንታኔ መስጫ
ዝምታ ነው መልሴ
ስላንቺ ብጠየቅ ,
ምንም ቃል የለኝ
ፀጋሽን ለማድነቅ
ገነት ገነትዬ
ልበል በጥቅሉ ,
ቋንቋ አልተፈጠረም
የሚገልፅሽ ቃሉ
እንጎቻሽ ሸጋ
ፍሬሽም ጣፋጭ ,
ትትና ደግነት
ከልብ የሚያመነጭ
ማን ይሉት ቋንቋው
አንቺን የመግለጫ ,
ከፍቅር የላቀ ፍቅርን
ትንታኔ መስጫ
ገኒዬ ገኒዬ
አለሁልህ በይኝ ,
በፈጠርሽ አምላክ
ቋንቋሽን አውሽኝ ,
ከ 'አፈቀርኩ ' ሽ ዕሚልቅ
ተንፍሼ ይውጣልኝ ::
Subscribe to:
Posts (Atom)